የጣና ሐይቅ የቀድሞ ተማሪዎች ህብረት- የ2014 ዓ.ም ዕቅድ

የጣናሐይቅ የቀድሞ ተማሪዎች ህብረት በየዓመቱ የሚያደርገውን  የገንዘብ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ለመጀመር ዝግጅቱን ጨርሷል። በእዚህ ለ5ተኛ ጊዜ በሚደረገው “የጣና ቤተሰብ ስኮላርሽፕ” ድጋፍ የሚከተሉትን ዕቅዶች ለማከናወን ታስቧል፦

1- የ5ተኛው ዙር የጣና ቤተሰብ ስኮላርሽፕ አሸናፊ  32 ተማሪዎችን መሸለም:-ከመስከረም – ሰኔ       
    ለያንዳንዳቸው 700 ብር  (10 ወር * 32 ተማሪዎች * 700 ብር)  – 224,000 ብር  (~$ 5,209)
2- ለ 250 የገንዘብ እጥረት ላለባቸው ሴት ተማሪዎች የንጽህና መጠባቂያ (Sanitary Pads) ለአንድ 
    ዓመት ማቅረብ – 85,000 ብር (~$1,977)
3- ለ4 ዓይነ ስዉራን ተማሪዎች ለትምህርታቸው የሚረዳ የድምፅ መቅጃ መሳሪያ መግዛት: 8,000
  ብር (~$186)
4- ወደ ዩኒቨርሲቲ ተመድበው ለሚገቡ እገዛ ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎች ድጋፍ ማድረግ እና የጣና ቤተሰብ ስኮላርሺፕ ተማሪዎች ህክምና መጠባበቂያ በጀት – 35,000 ብር  (~$814) 
5- የህብረቱን ስራዎች ባህር ዳር ላይ ለሚሰራልን ተማሪ የዓመት ደሞዝ ከመስከረም እስከ ነሐሴ –   
      1,200 ብር *12 ወር= 14,400 ብር (~$335)

በድምሩ 366,400ብር ወይም $8,521 ዶላር የሚገመት ወጪ በማድረግ እነዚህን ሥራዎች ለማሳካት ታቅዷል፡፡ እስካሁን ባለፉት 4 ዙሮች የነበረው የተማሪዎች እገዛ የተሳካው ይህን በጎ ሥራ የሰሙና የወደዱ ሁሉ ባደረጉት ያላሰለሰ የገንዘብ ፣ የሃሳብ እንዲሁም የጉልበት ድጋፍ ነው፡፡ በመሆኑም  5ተኛውን ዙር በተሻለ ሁኔታ ለማሳካት ጥሪ ስናቀርብ ድጋፋችሁ እንደማይለየን በመተማመን ነው።

Note : *Bank exchange rate used for estimate 1$ = 43 Birr

ኢትዮጵያ ውስጥ ያላችሁ ቀጥታ በሚከተሉት ህብረቱ የጋራ የባንክ አካውንቶች ማስገባት ትችላላችሁ፤
– የንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር፤ 1000408845622
 – የዳሽን ባንክ አካውንት ቁጥር፤ 5020904670002 

Or use other options here: https://tanahaikbdr.com/donate/

Tana Family Scholarship – 5th Round Gofundme – CLICK HERE

Social media page – THAN facebook page THAN Twitter page
Youtube channel – THAN Youtube channel 
To be a member please fill membership form – HERE 
CLICK HERE TO JOIN US ON VIBER

ከአክብሮት ጋር!

የህብረቱ አስተባባሪዎች! https://tanahaikbdr.com/about/

የ4ተኛው ዙር ሽልማት ተካሄደ

የ4ተኛው ዙር የጣና ቤተሰብ ስኮላርሺፕ አሸናፊ ተማሪዎች የሽልማት ሥነስርዓት ተካሄደ፡፡ ሥነስርዓቱ እሮብ ጥር 5 ቀን የቀድሞ ተማሪዎች ህብረት አስተባባሪዎች፣ መምህራንና ተሸላሚ ተማሪዎች በተገኙበት በጣና ሐይቅ ት.ቤት አዳራሽ ተካሂዷል፡፡ ለ32 ተማሪዎች የሽልማት ሰርተፊኬት የተሰጠ ሲሆን ሙሉ የትምህርት ዓመቱን ለትምህርት ወጪያቸው በየወሩ የገንዘብ ድጋፍ ይደረግላቸዋል፡፡ በተጨማሪም ህብረቱ በዚህ ዓመት ለ233 ሴት ተማሪዎች የሞዴስ አቅርቦት ማድረግ ጀምሯል፡፡ እንዲሁም እንደከዚህ በፊቱ ለተጨማሪ 10 ዓይነስውራን ተማሪዎች የድምፅ መቅጃ መሳሪያ ገዝቶ አቅርቧል፡፡

ተሸላሚ ተማሪዎችና የቀድሞ ተማሪዎች (ተጨማሪ ፎቶዎችን ከታች ይመልከቱ)

ለሥራው መሳካት የተባበሩትን የት.ቤቱን አስተዳደር፥ጣና የህትመትና ማስታወቂያ ድርጅትን፣ ጎዶሊያስ ሬስቱራንትንና ግሪን ፋርማሲን ከልብ እናመሰግናለን፡፡ እንዲሁም ዝግጅቱን የግል ጊዜያቸውን ሰውተው በአካል በመገኘት ያሳኩትን የቀድሞ ተማሪዎች ህብረት አስተባባሪዎች፡-

– ስለሺ ምንአየሁ፣ቴዎድሮስ ተሠራ፣ መሰረት እጅጉ፣ ራሄል ወንዴ፣ በሀይሉ ይርጋ፣ ምስጋናው ብርሃን፣ ሳሙኤል አልማው፣ ጌታ መሀሪ፣ ዮናታን ጎሳዬ፣ ሄኖክ ኃይለማርያም እና ያሬድ ምትኩን እናመሰግናለን፡፡ ለታናናሾቻችን ስኬት አብረን እንሥራ!!

የ2013 ዓ ም አራተኛው ዙር የጣና ቤተሰብ ስኮላርሺፕ አሸናፊ ተማሪዎች