የ7ኛው ዙር የጣና ቤተሰብ ስኮላርሺፕ አሸናፊ ተማሪዎች እውቅና የመስጠት መርሃግብር ተካሄደ

የዚህ ዓመት የጣና ቤተሰብ ስኮላርሺፕ (Tana Family Scholarship – TFS) የእውቅና መርሃ ግብር ታህሳስ 4 2016 ዓ/ም በጣና ሃይቅ ት/ቤት፣ አሸናፊ ተማሪዎች፣ የትምህርት ቤቱና የህብረቱ አመራሮች በተገኙበት  ተካሂዷል። 

በመርሃግብሩ ላይ ስለመርሃግብሩ አጭር ማብራሪያ  በህብረቱ የባህር ዳር ቢሮ አስተባባሪ አቶ አዱኛ ነጮ የተሰጠ ሲሆን ለእንግዶችና ለተሸላሚ ተማሪዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት አስተላልፈዋል። 

በመቀጠልም፣ እንግዶችን ያስተዋወቁ ሲሆን በዝግጅቱ ላይ የተገኙት፣ ከህብረቱ መስራችና አመራር  አንዱና በአሜሪካን አገር ነዋሪ የሆኑት ዶ/ር ጌታ መሃሪው እና የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር አቶ ሙጨ ባዘዘው ናቸው። 

ዶ/ር ጌታ ለተሸላሚ ተማሪዎች ባስተላለፉት መልዕክት፣ ህብረቱ ድጋፍ የሚያደርገው ተማሪዎችን ለማበረታታትና በድጋፍ ማጣት ምክንያት ጎበዝ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው እንዳይቀሩ ለማድረግ እንዲሁም ተማሪዎቹ ትምህርታቸውን ጨርሰው ወደስራ አለም ሲሰማሩ ተመሳሳይ ነገር ለሌሎች ድጋፍ እንዲያደርጉ አርአያ ለመሆን መሆኑን የገለጹ ሲሆን በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ተግዳሮቱቹን ተቋቁመው ለዚህ አመት የጣና ቤተሰብ ስኮላርሽፕ ሽልማት አሸናፊ በመሆናቸው አድናቆታቸውን ገልጸውላቸዋል።

በመጨረሻም የምስክር ወረቀት በእንግዶች የተሰጠ ሲሆን የትውውቅና የሻይ ቡና መርሃግብር በማከናወን ዝግጅቱ ተጠናቋል።

ይህ ድጋፍ እንዲሳካ በብዙ የደከማችሁ፣ የህብረቱ አባላትና አመራሮች፣ በጎ አድራጊዎች፣ የት/ቤቱ እመራሮችና የባህር ዳር አስተባባሪዎችን በሙሉ ከልብ እናመሰግናለን::  

ቀና ተሳትፏችሁን በቋሚነት ለመቀጠል በድረገፃችን ላይ የሚገኘውን የአባልነት ፎርም እንድትሞሉም እንጋብዛለን https://tanahaikbdr.com/contacts/

አድራሻዎቻችን፦

የዚህ ዓመት የጣና ቤተሰብ ስኮላርሽፕ አሸናፊ ተማሪዎች የሚከተሉት ናቸው። 

10ኛ ክፍል

  1. ተመስገን አማረ
  2. ሃና አዳነ
  3. ፋሲካ ሙሉ
  4. ነሲቡ በላይነህ
  5. አስፋው በቀለ
  6. ደመቀች ዋሴ
  7. ቤተልሄም ጋሻው
  8. ማሩ አለማንተ

11ኛ ክፍል

  1. ፍቅርተማርያም ታምሩ
  2. መቅደስ በላይነህ
  3. ሮዛ ጓዴ
  4. ፍሬገነት በቀለ
  5. ፍቃዱ ቤዛ
  6. ዳዊት ማሃባው
  7. ኤደን ገ/ሂወት
  8. ይትባረክ መልካሙ

12ኛ ክፍል

  1. አገር አምላክ
  2. መዝገቡ ውበት
  3. በሪሁን ምትኬ
  4. ቅድስት ማሩ
  5. አእምሮ ታደሰ
  6. ስማኮነ መላክ
  7. ስመኘው አጉማስ
  8. ልቦና እንደሻው

1ኛ ዓመት ኮሌጅ የሚገቡ

  1. ሃይለማሪያም ሉሉ
  2. ሙሉቀን ተሻገር
  3. ምንታምር በለጠ
  4. ፈንታሁን ሞላ
  5. መስፍን አስፋው
  6. መርድያ በለጠ
  7. መላከሰላም ላዋየው
  8. ኢዮብ መለሰ

በህብረት ለታናናሾቻችን የተሻለ ነገን እናውርስ!

ሪፖርተር፦ አዱኛ ነጮ ከባህር ዳር

የ7ኛው ዙር የጣና ቤተሰብ ስኮላርሺፕ አሸናፊ ተማሪዎች ታወቁ

የጣና ቤተሰብ ስኮላርሺፕ (Tana Family Scholarship-TFS) ፣ በጣና ሐይቅ የቀድሞ ተማሪዎች ህብረት (Tana haik Alumni Network-THAN) እና በበጎ አድራጊዎች የገንዘብ ድጋፍ አማካኝነት፣ በየዓመቱ  በክፍል ውጤታቸውና በቤተሰብ ገቢ ሁኔታቸው የተመረጡ የ10ኛ፣ 11ኛ፣12ኛና ወደ ዩኒቨርስቲ መግቢያ ያገኙ 1ኛ ዓመት ታዳጊ የጣና ሃይቅ ትምህርት ቤት ተማሪዎችን ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያግዝ ፕሮግራም ነው:: 

በዚህ መሰረት፣ በዚህ ዓመትም የጣና ሐይቅ የቀድሞ ተማሪዎች ኅብረት ባወጣው መስፈርት መሰረት 7ኛው ዙር የጣና ቤተሰብ ስኮላርሺፕ አሸናፊ 32 ተማሪዎች ተመርጠዋል፡፡

የአሸናፊዎች ዝርዝርም በክፍል በክፍል እንደሚከተልው ቀርቧል። 

10ኛ ክፍል

  1. ተመስገን አማረ
  2. ሃና አዳነ
  3. ፋሲካ ሙሉ
  4. ነሲቡ በላይነህ
  5. አስፋው በቀለ
  6. ደመቀች ዋሴ
  7. ቤተልሄም ጋሻው
  8. ማሩ አለማንተ

11ኛ ክፍል

  1. ፍቅርተማርያም ታምሩ
  2. መቅደስ በላይነህ
  3. ሮዛ ጓዴ
  4. ፍሬገነት በቀለ
  5. ፍቃዱ ቤዛ
  6. ዳዊት ማሃባው
  7. ኤደን ገ/ሂወት
  8. ይትባረክ መልካሙ

12ኛ ክፍል

  1. አገር አምላክ
  2. መዝገቡ ውበት
  3. በሪሁን ምትኬ
  4. ቅድስት ማሩ
  5. አእምሮ ታደሰ
  6. ስማኮነ መላክ
  7. ስመኘው አጉማስ
  8. ልቦና እንደሻው

1ኛ ዓመት ኮሌጅ የሚገቡ

  1. ሃይለማሪያም ሉሉ
  2. ሙሉቀን ተሻገር
  3. ምንታምር በለጠ
  4. ፈንታሁን ሞላ
  5. መስፍን አስፋው
  6. መርድያ በለጠ
  7. መላከሰላም ላዋየው
  8. ኢዮብ መለሰ

ይህ ድጋፍ እንዲሳካ በብዙ የደከማችሁ፣ የህብረቱ አባላትና አመራሮች፣ በጎ አድራጊዎች፣ የት/ቤቱ እመራሮችና የባህር ዳር አስተባባሪዎችን በሙሉ ከልብ እናመሰግናለን::  

ቀና ተሳትፏችሁን በቋሚነት ለመቀጠል በድረገፃችን ላይ የሚገኘውን የአባልነት ፎርም እንድትሞሉም እንጋብዛለን https://tanahaikbdr.com/contacts/

አድራሻዎቻችን፦

ስለህብረቱና ስለሚሰራቸው ስራዎች ይበልጥ ለማወቅ የሚከተለውን ብሮሸር መመልከት ይቻላል።

የ2015 6ኛው ዙር አሸናፊዎች ፎቶዎች

በህብረት ለታናናሾቻችን የተሻለ ነገን እናውርስ!

የህብረቱ አስተባባሪዎች