ለሁለተኛው ዙር የጣና ቤተሰብ ስኮላርሺፕ ስኬታማ እንዲሆን በመቆም ላበረታታችሁን፤ ቃላችንን አምናችሁ ገንዛባችሁንና ጊዜአችሁን ሳትሳሱ ለደገፋችሁን የከበረ አክብሮታችን ይድረሳችሁ። ጣናሃይቅ ት.ቤት ባትማሩም በሃሳባችን ተስማምታችሁ ድጋፍ ላደረጋችሁልን በሙሉ እጅግ በጣም እናመሰግናለን። የገንዘብ የማሰባሰብ ዘመቻው ጥቅምት 30,2011 (November 9,2018) ይጠጥናቀቃል::
ባለፈው ዓመት በሁላችሁም ስጦታ የመጀመሪያው ዙር ስኮላርሺፕ በልዩ ሁኔታ ተሳክቷል:: 24 ተማሪዎችን በየወሩ በወጪ ደግፈናል: ለ100 ሴት እህቶቻችን ንፅህና መጠበቂያ በየወሩ አቅርበናል: ለ2 ዓይነስውራን ወንድሞቻችን ለትምህርታቸው የሚረዳ ዘመናዊ የድምፅ መቅጃ ገዝተን ልከናል: የት/ቤቱን ቤተ-መጻህፍት ካለበት የመጽሃፍ ዕጥረት ለመታደግ “አንድ መጽሃፍ ለአንድ ተማሪ” በሚል የድጋፍ ዘመቻ ከ620 በላይ መጻህፍት (reference books) ለትምህርት ቤቱ ለግሰናል::
ትቤቱንና ተማሪዎችን ለመደገፍ የሚሰሩ ሌሎች ስራዎንን ለመደገፍ ከእኛ ጋር እንደምትሰሩ በሙሉ ልባችን እንተማመናለን። ቀና ተሳትፏችሁን በቋሚነት ለመቀጠል በድረገፃችን ላይ የሚገኘውን የአባልነት ፎርም እንድትሞሉም እንጋብዛለን(https://tanahaikbdr.com/contacts/)
ድር ቢያብር ነውና ብሂሉ የሁሉም ሰው ተሳትፎ ለስኬት ያበቃናል:: በህብረት ለታናናሾቻችን የተሻለ ነገን እናውርስ::በጋራ ዓላማችን እንደምናሳካ እርግጠኞች ነን!
- መላከሰላም ገዳሙ
- ኪዳነማርያም ዉበቴ
- እህተሙሴ ነብዩ
- አበቡ ዉበቴ
- ጸደይ አበበ
- ፍቅርአዲስ አስቻለ
- ገሊላ ብዙአየሁ
- ዳዊት አዳሙ
- በረከት አዳሙ
- ዳኛቸዉ ተሰማ
- ብርሃነመስቀል ወርቁ
- ፍቅሩ ውቤ
- ያብስራ ፍቃዴ
- ሜሮን ማዘንጊያ
- አበበ ወሌ
- ዮናስ አበበ
- ሙላት ጌጡ
- አምሳሉ አሞኝ
