የአራተኛው ዙር የጣና ቤተሰብ ስኮላርሺፕ አሸናፊ ተማሪዎች ታወቁ

በዚህ ዓመት ስለሀገራችን የምንሰማው ነገር በጣም አሳዛኝ ሆኗል፤ የቀድሞ የጣና ሐይቅ ተማሪዎች ህብረትም ሀገራችን ከዚህ ሁሉ ችግር ተላቃ ሁሉም ዜጋ በፈለገበት ቦታ ያለስጋት የሚኖርበት ዘመን እንዲመጣ ከልብ ይመኛል:: ሁላችንም በያለንበት የማህበረሰባችን ችግር መፍትሄ አካል ለመሆን የተቻለንን እናድርግ::

ከጥቂት ወራት በፊት እደተገለጸው የ2013 ዓ.ም. ዕቅዶችን ለማሳካት ከአባላት ገንዘብ ተሰብስቧል፡፡ይህም የዚህን ዓመት አቅማችንን ለማሳደግ ስላገዘን በዚህ ዓመት የሚከተሉተን ማሻሻያዎች ለማድረግ አስተባባሪዎች ወስነዋል::
የ2013 ዓ.ም የጣና ቤተሰብ ስኮላርሽፕ አሸናፊ ተማሪዎችን ብዛት ከ24 ወደ 32 ያሳደግን ሲሆን (ወቅታዊውን ወረርሽኝ በማስመልከት የዚህ ዓመት ማጣሪያ ሂደት በልዩ ሁኔታ ታይቶ ነባር ተማሪዎችን ይዘን ጥቂት አዳዲስ ተማሪዎችን ጨምረናል)፤  ለሴት ተማሪዎች የሚቀርበው የንጽህና መጠበቂያ (Sanitary Pads) ተጠቃሚዎች ቁጥርም ከ150 ወደ 233 ከፍ እንዲል ተደርጓል። ለዚህ እድገት ሁላችሁም አስተዋጽኦ አድርጋችኋልና ከልብ እናመሰግናለን!!

ቀደም ብሎ እንደተገለፀውም ህብረቱ በ18ሺህ ብር ወጪ 5ሺ ሊትር የሚይዝ የውሃ ማጠራቀሚያ (water tank) ለትምህርት ቤቱ አስረክቧል፡፡ እንዲሁም ከዚህ በፊት እንደተደረገው ለተጨማሪ 10 ዓይነስውራን ተማሪዎች የድምፅ መቅጃ መሳሪያ ለመስጠት በዝግጅት ላይ ነው፡፡
በዚህ መሰረት ለዚህ ዓመት የጣና ቤተሰብ ስኮላርሺፕ የሚከተሉት ተማሪዎች አሸናፊ ሆነው ተመርጠዋል።

የ2013 ዓ.ም አራተኛው ዙር የጣና ቤተሰብ ስኮላርሺፕ አሸናፊ ተማሪዎች

10ኛ ክፍል:

1- ሜሮን ክንዴ
2- ፍቅር ይልቃል
3- ሙሉቀን ተሻገር
4- ፍቅርተ ጌታቸው
5-  ኃይለማርያም ልዑል
6- ሀብታሙ ውብሸት
7- ቢኒያም አላምረው
8- ፋሲካው ቢያዝን

11ኛ ክፍል :

1- ቤቴልሃም ደባሱ
2- ቤቴልሄም ጌታቸው
3- አልማዝ መንጌ
4- ሙራድ ኑሩ
5- ጠብቀው ውበት
6- ሀይማኖት ምናለ
7- ሰለሞን ነጋ
8- አማኑኤል ፍስሀ

12ኛ ክፍል:

1- ሕይወት ይልቃል
2- ኤልሳቤት ጌታቸው
3- ሠርካለም እውነቴ
4- እህተሙሴ ነብዩ
5- ሙሉቀን ዘመነ
6- ደመቀ አስቻለ
7- መታደል ሀይማኖት
8- ብሩክ አሰፋ

1ኛ ዓመት ኮሌጅ የሚገቡ:

1- ሊዲያ ነብዩ
2- ማህሌት ሰሙ
3- ገሊላ ብዙአየሁ
4- ብርሃነመስቀል ወርቁ
5- አወቀ ጋሻው
6- ጴጥሮስ ጌታቸው
7- ሙላቱ ዘሪሁን
8- መልካሙ ሙሉአለም

በዚህ በጎ ሃሳብ ላይ በማስተባበር የተሳተፋችሁትን ሁሉ እናመሰግናለን፡፡ በተለይም የባህርዳር አስተባባሪዎችን:-

  • መሰረት አጅጉ
  • ስለሺ ምንአየሁ
  • መላኩ ባሳዝነው
  • በሀይሉ ይርጋ እና 
  • ያሬድ ምትኩ

እንዲሁም የትምህርት ቤቱን አስተዳደር እናመሰግናለን፡፡

ት/ቤቱንና ተማሪዎችን ለመደገፍ የሚሰሩ ሌሎች ስራዎችን ለመደገፍ ሁላችንም አብረን መስራት እንደምንቀጥል በሙሉ ልባችን እንተማመናለን። ቀና ተሳትፏችሁን በቋሚነት ለመቀጠል በድረገፃችን ላይ የሚገኘውን የአባልነት ፎርም እንድትሞሉም እንጋብዛለን (https://tanahaikbdr.com/contacts/)

በዚህ ቪዲዮ የመጀመሪያው ዙር የጣና ቤተሰብ ስኮላርሺፕ (2010ዓ.ም) ተሸላሚ የነበሩና በቀድሞ ተማሪዎች ህብረት ሲታገዙ የነበሩ ተማሪዎች ሃሳባቸውን ያካፍላሉ።
https://youtu.be/Z1eRtSnF0cU

ለበለጠ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያ ገፆቻችንን ይከተሉን።

Social media page – THAN facebook page / THAN twitter 

Youtube channel – THAN Youtube channel

CLICK HERE TO JOIN US ON VIBER

በህብረት ለታናናሾቻችን የተሻለ ነገን እናውርስ!

የህብረቱ አስተባባሪዎች

የጣና ሐይቅ የቀድሞ ተማሪዎች ህብረት- የ2013 ዓ.ም እቅድ

የቀድሞ የጣና ሐይቅ ተማሪዎች ህብረት በየዓመቱ በዚህ ወቅት የምናደርገውን የጎፈንድሚ ገንዘብ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር በወቅታዊው ሁኔታ ምክንያት በተለመደው መልኩ ላለማካሄድ ወስነናል፡፡በዚያ ፋንታ አስተባባሪዎች፣አባላትና የማህበሩ ወዳጆች በቀጥታ ወደማህበሩ አካውንት መዋጮ የሚያስገቡበትን አማራጮች አዘጋጅተናል፡፡ የቀጣዩን ዓመት ወጪ ከዚህ መዋጮ እና ከባለፈው ዓመት መጠባበቂያ በጀት በመጠቀም ለመሸፈን አስበናል፡፡ ህብረቱ የሚከተሉትን የ2013 ዓ/ም  ሥራዎች ለማከናወን አቅዷል፦
  1. የ4ተኛው ዙር የጣና ቤተሰብ ስኮላርሽፕ አሸናፊ  24 ተማሪዎችን መሸለም:-ከመስከረም – ሰኔ ለያንዳንዳቸው 500 ብር  (10 ወር * 24 ተማሪዎች * 500 ብር)  – 120,000 ብር (~$3,410)(በዚህ አጋጣሚ በዘጠነኛ ክፍል 6 ተማሪዎች ፋንታ ከጣና ሐይቅ ወደ ኮሌጅ የሚያልፉ 6 የአንደኛ ዓመት ተማሪዎችን ለማገዝ ተወያይተናል፡፡ ስለዚህ 24ቱ ተማሪዎች ከ10ኛ፣11ኛ፣12ኛና ከአንደኛ ዓመት ኮሌጅ የሚመረጡ ይሆናሉ)
  2. ለ 150 የገንዘብ እጥረት ላለባቸው ሴት ተማሪዎች የንጽህና መጠባቂያ (Sanitary Pads) ለአንድ አመት ማቅረብ – 30,000 ብር (~$850)
  3. ለ10 ዓይነ ስዉራን ተማሪዎች ለትምህርታቸው የሚረዳ የድምፅ መቅጃ መሳሪያ መግዛት  – 21,150 ብር (~$600)
  4. ለአካል ጉዳተኛ የጣና ቤተሰብ ስኮላርሽፕ ተሸላሚዎች የክረምት ሁለት ወራት ተጨማሪ እርዳታ ማድረግ እና የ24ቱ ተማሪዎች ህክምና መጠባበቂያ በጀት – 5,300 ብር (~$150)
  5. የህብረቱን ስራዎች ባህር ዳር ላይ ለሚሰራልን ተማሪ የዓመት ደሞዝ ከመስከረም እስከ ነሐሴ – 1,000*12ወር= 12,000 ብር (~350)

በአጠቃላይ የ2013 ዓ.ም የበጀት እቅዳችን 188,450 ብር (~$5,350 USD) ይሆናል፡፡

በተጨማሪም ከዚህ ዓመት ዕቅዶች መካከል ሊሰሩ ታስበው ባለው ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት ለሌላ ጊዜ እንዲተላለፉ የተደረጉ ሁለት ሥራዎች አሉ፦

  • ለትምህርት ቤቱ የመጠጥ ውሃ ማጠራቀሚያ ማስገባት (Water Tank) እና
  • በት/ቤቱ የሚገኘውን የህብረቱን ቢሮ ማስጠገንና መጠቀም ናቸው፡፡ የህብረቱ ዋና ዓላማ ተማሪዎች ላይ መስራት ስለሆነ እነዚህን ከዋናው የዓመት በጀት ውስጥ ሳናካትት በተጠባባቂነት እንይዛቸዋለን፡፡ 

በየአመቱ ለመክፈል ቃል የገባችሁ አባሎች እንዲሁም በዚህ አመት ለመሳተፍ ለምትፈልጉ የማህበሩን  Zelle Account (202 413-4946) ወይም በድረ ገፃችን የቀረቡ አማራጮችን መጠቀም ትችላላችሁ (https://tanahaikbdr.com/donate/

ተማሪዎቹንና ትቤቱን ለመደገፍ ሁላችንም አብረን እንደምንቆም በሙሉ ልባችን እንተማመናለን። ቀና ተሳትፏችሁን በቋሚነት ለመቀጠል በድረገፃችን ላይ የሚገኘውን የአባልነት ፎርም እንድትሞሉም እንጋብዛለን፡፡(https://tanahaikbdr.com/contacts/)

ከአክብሮት ጋር!

የህብረቱ አስተባባሪዎች! https://tanahaikbdr.com/about/

THAN-PLAN-2013

ለበለጠ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያ ገፆቻችንን ይከተሉን።

Social media page – THAN facebook page / THAN twitter 

Youtube channel – THAN Youtube channel

CLICK HERE TO JOIN US ON VIBER