Report on April 28,2013 Skype Meeting

April 28, 2013 Skype Meeting Report

  1. Former students from Ethiopia,Canada,USA,Finland and UK of different batches started the meeting by introducing each other and with updates on the previous tasks.
  2. According to the report from our members in Bahir Dar the expansion of additional internet lines is being done by former students in Bahir Dar, full report will be posted soon.
  3. New ideas were raised for book collection and fundraising events to improve the facility of our new library.
  4. It is agreed to work on the consistency of rewarding best students and holding annual dinner program for teachers. Annual dinner programs for former teachers  will be organized by a different batch each year to give everyone the chance to participate as Tana Family member.
  5. The next Ethiopian soccer tournaments will recently be held in DC, USA and Europe. So our members abroad are planning to organize an event and reach out more former Tana graduates.
  6. Finally all attendees shared  tasks till the next meeting (May 26,2013). Additional updates will be posted by individuals on the Facebook page. All Tana Family members are highly encouraged to share ideas, comment on posts and participate on the events.

Tana Alumni Skype Meeting Report

መጋቢት 22.2005/ ማርች 31.2013

(Click here to read in PDF)

የጣና ሐይቅ የቀድሞ ተማሪዎች ከሰሜን አሜሪካና አውሮፓ በስካይፕ ስብሰባው ላይ ተገኝተዋል። ቤተሰባዊ ስሜት የነበረው ውይይት በሰላምታና ደህንነትን በመጠያየቅ ተጀምሯል። ዳዊት (አላባማ) ከጥቂት ወራት በፊት ኢትዮጲያ በነበረው ቆይታ የነበረውን ስሜትና የት.ቤቱን ይዞታ አካፍሎናል። የተነሱ ጥያቄዎች ላይም በሁሉም ተሰብሳቢ ውይይት ተደርጓል። እንደአጀንዳ ከተያዙት ነጥቦች ውስጥ እነዚህን ተነጋግረናል፦

1. የላይብረሪያን ደሞዝ

በቀድሞ ተማሪዎች ስም ሥራ ለጀመረው ላይብረሪ ላይብረሪያን እንደሚያስፈልግ ከዚህ በፊት ተገልጾ ነበር (የፌቡ መልዕክት ከኢትዮጵያ)።ዳዊት በአካል ተገኝቶ ያየውን የላይብረሪውን ሁኔታ አካፍሎናል። ተወያዮቹ በደሞዝ የሚያገለግል አንድ ላይብረሪያን ለጊዜው በቂ እንደሆነ ተወያይተዋል። በትርፍ ጊዜያቸው አገልግሎቱን የሚያግዙ (የቤ.መጽሐፍት ክበብ አባል የሆኑ) ተማሪዎችን ማሳተፍ እንደ ተጨማሪ ነጥብ ተይዟል። ደሞዙን በቀጣይነት ለመሸፈን ምን መደረግ እንዳለበትም ተወያይተናል።በዓመታዊው የሰ.አሜሪካ የእግር ኳስ ፕሮግራም ላይ መገናኘትና ዓላማውን ገልፀን የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ልናደርግ እንደምንችል ሀሳብ ተሰጥቷል። እንደተጨማሪ የቀድሞ ተማሪዎች ወርሀዊ መዋጮም ቢታሰብበት ለምናደርገው እገዛ ቀጣይነት ጥሩ መሆኑ ተነስቷል። ተወያዮች በተነሱ ነጥቦች ላይ ሀሳብ ተለዋውጠን እንደመነሻ የሚሆን ገንዘብ ($200) ለመላክ ተስማምተናል። ስብሰባው ላይ መገኘት ላልቻሉና መሳተፍ ለሚፈልጉ የቀድሞ ተማሪዎችም በፌቡ ለማሳወቅ ተስማምተናል። ለት.ቤቱ ገቢ ማስገኛ የሚሆኑ መንገዶች ላይ አዳዲስ ሀሳቦች ተነስተው ወደፊት ይበልጥ ልንወያይ አቅደናል።

2. መጽሐፍትና ኢንተርኔት

ታናናሾቻችን ጥሩ ትምህርታዊ መረጃ የሚያገኙበት መንገድ ማመቻቸት ከተያዙት ዕቅዶች አንዱ ነው። ለዚህ የሚያስፈልጉ መጽሐፍትን እንዴት ማሰባሰብ እንደሚቻል ተወያይተናል። መጽሐፍትን አሰባስቦ በ’ኮንቴነር’ መላክ ወጪው ከፍተኛ ስለሆነ ለጊዜው መላኪያ መንገዶችን ማመቻቸት የላኪው ድርሻ ይሆናል። የኢ.አ.መንገድ በሚያደርገው የቀጥታ በረራ የሚፈቅደው የማጓጓዣ መንገድ አለ የሚል ሀሳብ ተነስቷል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ዲ.ሲና አካባቢው ያሉ ተወያዮች ኃላፊነት ወስደዋል።

የኢንተርኔት መስመር በቀድሞ ተማሪዎች አማካኝነት ወደ መጀመሪያው ላይብረሪ ገብቷል። ይህንን መስመር ወደ ሁለተኛው ላይብረሪም መውሰድ እንደሚያስፈልግ ውይይቱ ላይ ተነስቷል።

3. አቅም ማሳደግ

የተማሪዎችን አቅም ለማሳደግ በቀድሞ ተማሪዎች የሚሰጥ ትምህርት (Tutorial Class) ስለማመቻቸት ተወያይተናል። እንደመነሻ ለተወሰኑ ተማሪዎች መሰረታዊ የኮምፒውተር ትምህርት መስጠት እንደሚቻል ሀሳብ ቀርቧል። እገዛው ተማሪዎቹን ወደኮሌጅና ዩኒቨርሲቲ ሲገቡ የበለጠ ተወዳዳሪ ሊያደርጋቸው እንደሚችል ውይይቱ ላይ ተነስቷል። ሀሳቡን ኢትዮጵያ ከሚገኙ የቀድሞ ተማሪዎች ጋር ለመወያየት ታቅዷል።

4. ተጨማሪ

በቅርቡ ስለነበረው የመጽሐፍት ሥጦታና ተማሪዎችን የማበረታታት ፕሮግራም ተወያይተናል። የዝግጅቱ መንፈስና ውጤቱም ጥሩ እንደነበር ተነስቷል። በቦታው ላልነበርን ተጨማሪ ፎቶዎች የፌቡ ገፁ ላይ ይለቀቃሉ።በጊዜው የታዩት መፍትሄ የሚያስፈልጋቸው ክፍተቶች ተነስተዋል። ከአገልግሎት ውጪ የሆኑ ‘ብላክቦርዶች’፣ የክፍል መስኮቶች፣ ‘ላይቲንግ’ እንደምሳሌ ተጠቅሰዋል። የታዩትን ወቅታዊ ጉድለቶች ይበልጥ ለመረዳትና ለመፍታት በጽሑፍ እንዲያዙ ታቅዷል።

በመጨረሻ ውይይቱ ወርሀዊ እንዲሆን (በወር የመጨረሻ እሁድ) ተነጋግረን ተሰነባብተናል። ለመሳተፍ ከቻሉ የጣና ቤተሰብ አባል ይሁኑ፣ ኑና ለታናናሾቻችን ስኬት አብረን እንሥራ።