ዛሬ መጋቢት 30/2004 Today Apr 8/2012

ዛሬ

የቀድሞ ተማሪዎች፣ መምህራንና ተማሪዎች ግቢውን በማፅዳት ተሳትፈዋል። ሁሉንም እናመሰግናለን።

በአባላቱ ተሳትፎ አንዱ ዕቅድ ወደ ተግባር መሻገር ጀምሯል። የቤተመጽሐፍቱ ወንበሮች እየተዘጋጁ ነው። ልዩ ምስጋና ለመላኩ ባሳዝነውና ለቀበሌ 14 ልጆች (አዳነች መሀመድ፣ ጌትነት ደሳለኝና መሰረት ንጉሴ)።

ከመምህራን ጋር የሚደረገው የገቢ ማሰባሰቢያ እራት ፕሮግራም ለሐሙስ ተላልፏል። እስካሁን ላልተሳተፍን ተጨማሪ ጊዜ አለን።


Today


Great job everyone! Members of alumni, teachers and students took part in cleaning the school compound! 

Thanks to our members, we are on our way to see a dream come true. The production of chairs has began. Melaku Basazinew, Adanech Mohammed, Getnet Desalegn and Meseret Nigussie your special effort will be remembered!

The fundraising dinner pgm is postponed to next Thursday, the bright side is there is more time for those of us who did not participate yet.

ዜና – News Update

የ94 ባች 10ኛ ዓመት ምረቃ በዓላቸውን ለማክበር በዝግጅት ላይ ናቸው።

በዓሉን አስመልክቶ ሊሠሩ ከታሰቡት መካከል 80 ወንበሮችንና ተጨማሪ መጽሐፍትን ለላይብረሪው ማቅረብ፣ ለንባብም ዝግጁ እንዲሆን ማድረግ ይገኝበታል (ለበለጠ መረጃ ዝርዝር ዕቅዱን /Draft action plan/ ይመልከቱ)፤ ዕቅዱን ለማየት የቀረበውን ሊንክ ከተከተሉ በኋላ download from sendspace የሚለውን አማራጭ ይከተሉ።


ለመጪው ቅዳሜ (መጋቢት 29/Apr.7) የገቢ ማሰባሰቢያ እራት ፕሮግራም ከቀድሞ መምህራን ጋር፣
እሁድ (መጋቢት 30/Apr 8) ት.ቤቱን በህብረት ከሁሉም የት.ቤቱ አካላት ጋር የማፅዳት ፕሮግራም 
ቅዳሜ (ሚያዚያ 6/Apr 14) 10ኛ ዓመት በዓሉን በት.ቤቱ ላይብረሪ የማክበር ዕቅድ ተይዟል።
ለእራት ፕሮግራሙ አስተባባሪ ኮሚቴው እንዲካፈሉ ከጋበዛቸው መምህራን ሌላ ‘መምህር እከሌን እኔ እራት መጋበዝ እፈልጋለሁ’ ብሎ ማሳወቅ ይቻላል (የተወካዮቹ አድራሻ ዕቅዱ ላይ አለ)። በዝግጅቱ ላይ አፋጣኝ መፍትሔ ለሚያስፈልጋቸው ችግሮች የሚሆን የገቢ ማሰባሰብ (Fund raising) ይካሄዳል።
የእራት ዝግጅቱን በቀጥታ በዚህ ብሎግ የመዘገብ ዕቅድ ተይዟል። እንዳያመልጠን!